Sunday, May 30, 2010

መለከት

ካህናቱም በየሥርዓታቸው፥ ሌዋውያኑም ደግሞ። ምሕረቱ ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ የሚለውን የዳዊትን መዝሙር እየዘመሩ፥ ንጉሡ ዳዊት እግዚአብሔርን ለማመስገን የሠራውን የእግዚአብሔርን የዜማ ዕቃ ይዘው ቆመው ነበር ካህናቱም በፊታቸው መለከት ይነፉ ነበር እስራኤልም ሁሉ ቆመው ነበር። መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 7:6
የማንም እጅ አይንካ ነገር ግን የሚነካው ሁሉ ይወገራል፥ ወይም በፍላጻ ይወጋል እንስሳ ወይም ሰው ቢሆን አይድንም በላቸው። ሳያቋርጥ የመለከት ድምፅ ሲነፋ በዚያን ጊዜ ወደ ተራራው ይውጡ................
እንዲህም ሆነ በሦስተኛው ቀን በማለዳ ጊዜ ነጐድጓድና መብረቅ ከባድም ደመና እጅግም የበረታ የቀንደ መለከት ድምጽ በተራራው ላይ ሆነ በሰፈሩም የነበሩት ሕዝብ ሁሉ ተንቀጠቀጡ። ኦሪት ዘፍጥረት 19:13-16
ሙሴም ከየነገዱ አንድ አንድ ሺህ ወደ ጦርነት ሰደደ እነርሱንና የካህኑን የአልዓዛርን ልጅ ፊንሐስን ወደ ጦርነት ሰደዳቸው የመቅደሱንም ዕቃ የሚነፋውንም መለከት በእጁ ሰጠው።ኦሪት ዘኍልቍ 31:6

No comments:

Post a Comment